በኮልፌ ቤቱ የፈረሰበት አባወራ በጅብ ሲበላ አንዲት ወላድ በድንጋጤ ህይወቷ አለፈ

ዳዊት ሰለሞን

‹‹ቪዛ ይሰጠንና ወደ ሱማሌያ ቢሆንም እንሂድ›› ቤታቸው የፈረሰባቸው

በኮልፌ ቀራኒዮ አለም ባንክ አካባቢ ህገ ወጥ የመሬት ወረራ በማድረግ ቤቶችን ሰርታችኋል የተባሉ ዜጎች ቤቶቻቸው በላያቸው ላይ በሀይል ፈርሶ ንብረታቸው መወረሱን አመለከቱ፡፡ ከ15.000 የሚልቁ ነዋሪዎች በሚገኙበት አለም ባንክ አካባቢ ሰዎቹ አነስተኛ መጠለያ ያረፉባቸውን ቤቶች ከገበሬዎች ላይ በመግዛት መኖር ከጀመሩ አመታት መቆጠሩን ያስረዳሉ፡፡ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ልከውና ወደ ስራ በተሰማሩበት ቅጽበት ከጸጥታ ሰራተኞች ጋር አካባቢውን የወረሩት አፍራሽ ግብረ ሃይሎች መኖሪያ ቤቶቹን ማፍረሳቸውን በሀዘን ተውጠው ገልጸዋል፡፡ ቤቶቹ በድንገት መፍረሳቸውን በመቃወም ድምጻቸውን ያሰሙ የአካባቢው ነዋሪዎች በፖሊሶች ክፉኛ መደብደባቸውንና መወሰዳቸውን የአይን እማኞች አስረድተዋል፡፡ቤቷ ሲፈርስ የደነገጠች እመጫት ወዲያኑ ህይወቷ ሲያልፍ ቤቱ በመፍረሱ መሄጃ ያጣ አባወራ ላስቲክ ዘርግቶ በተኛበት ጅብ ጎትቶት ወስዶት በልቶታል፡፡በጅብ የተበላው አባወራ ስርዓተ ቀብርም ዛሬ መፈጸሙ ታውቋል፡፡ ቤታቸው ፈርሶ ለጎዳና እንደተዳረጉ የሚናገሩ ሰዎች‹‹ኢትዮጵያዊነታችን ተሰርዟል፣ቪዛ ይሰጠንና ሌላው ቢቀር ወደ ሶማሊያ እንድንሄድ ይደረግ ›› ብለዋል፡፡

Finote nestanet

ተጨማሪ ያንብቡ:  አቢይ አህመድ በዛሬው የፓርላማ ውሎው የፖለቲካ አላዋቂነቱና ድንቁርናው ለይቶለት ፍጥጥ ብሎ በመውጣቱ ብዙዎች “የአእምሮ በሽተኛ” እያሉት ነው

2 Comments

  1. It is sad to see the displacement of Ethiopians to give away their land to TIGRIANS

  2. Removing this dictatorial regime is the only solution.The EPRDF/TPLF elites and its cronies have built high rise by evicting the less fortunate ones and we are silent. How long are we silent while they are obliterating us in a tandem? Unless we break the silent and stand hand-in-hand against this dictatorial regime, we will be remain enslave for a generation to come. Elders, Prominent Political leaders, Scholars, Human and Political activist, International award winner Journalist, Religious figures, bloggers, students have been languishing in prison, hundreds of thousands are fleeing Ethiopia and Ethiopia is reduced to a police state. So what are we waiting for? Are we waiting the west to come and liberate us from EPRDF/TPLF Machiavellan ruling? or are we waiting the Almighty to descend and emancipate us?
    No one come to fight our fight unless we united and fight our fight.

Comments are closed.

Share