May 13, 2014
6 mins read

የሀያኛውን ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ፖለቲካ የቀየሩ አነስተኛ ሰነዶች- (በብዙዎች ጥያቄ የተደገመ)

(አፈንዲ ሙተቂ)


ይህንን አነስተኛ መጣጥፍ ከዚህ በፊት (በታህሳስ ወር 2006) ለጥፌው ነበር፡፡ ነገር ግን በርካታ ወዳጆቼ ከፌስቡክ ግድግዳህ ላይ ልናገኘው አልቻልንም” ስላሉኝ እንደገና መድገሙ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ለፍለጋ ቀለል የሚለው ብሎግ ስለሆነ በኔ ብሎግ ላይም እለጥፈዋለሁ፡፡

እነዚህ ሰነዶች በ20ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አሳርፈዋል በማለት በዝርዝሩ ውስጥ የያዝኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ዝርዝሩ በሌሎች ምሁራንም ሆነ የጥናት ተቋማት እውቅና አልተሰጠውም፡፡ ማንም ሰው የክፍለ ዘመኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ አካሄድ ገምግሞ ከፍተኛ ተጽእኖ አሳድረዋል ያላቸውን ሰነዶች ሊጠቁም ይችላል፡፡ እኔም ይህንኑ ነው ያደረግኩት፡፡

ሰነዶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡

1. አዕምሮ ጋዜጣ- 1904
2. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ህገ-መንግሥት- 1923
3. የኤርትራ ፌዴሬሽን ህገ-መንግሥት 1944
4. የተሻሻለው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ህገ-መንግሥት- 1948
5. የጀብሃ ቻርተር- 1954
6. የሜጫና ቱለማ ማህበር መተዳደሪያ ደንብ-1955
7. የብሄር ጥያቄ በኢትዮጵያ (በዋለልኝ መኮንን የተጻፈ ጽሑፍ)-1961
8. “ንህናን ዓላማናን”(እኛና ዓላማችን)- ሻዕቢያ ከጀብሃ የተገነጠለበት አነስተኛ ጥራዝ-1964
9. ደርግ ስልጣን የያዘበት አዋጅ- መስከረም 2/1967
10. የገጠር መሬትን ለህዝብ ያደረገው አዋጅ- የካቲት 25/1967
11. ዲሞክራሲያ ጋዜጣ (የኢህአፓ መመስረት ይፋ የሆነበት የፓርቲው ህቡዕ ጋዜጣ)- ነሐሴ 27/1967
12. የተሓሕት/ህወሐት ማኒፌስቶ- የካቲት 1968
13. የብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ አብዮት ፕሮግራም አዋጅ- ታህሳስ 1968
14. የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽ/ቤት የተመሰረተበት አዋጅ- ሚያዚያ 1968
15. የኦነግ የፖለቲካ ፕሮግራም- ሰኔ 1968
16. ኢሰፓአኮ የተቋቋመበት አዋጅ-ሰኔ 1971
17. ኢሰፓ የተመሰረተበት አዋጅ- መስከረም 1977
18. የኢህዲሪ ህገ-መንግሥት-ጳጉሜ 1979
19. የኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ቻርተር- ሀምሌ 1983
20. የፕሬስ አዋጅ- የካቲት 1984
21. የክልሎች ማቋቋሚያ አዋጅ- ጥቅምት 1985
22. ኢትዮጵያ ለኤርትራ ነጻነት እውቅና የሰጠችበት ደብዳቤ (በአቶ መለስ ዜናዊ የተጻፈ)-ሚያዚያ 1985
23. የኢፌዴሪ ህገ-መንግሥት- ህዳር 29/1987
24. የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ያበቃበት የአልጀርስ ስምምነት -ታህሣስ 1993
25. አብዮታዊ ዲሞክራሲና ቦናፓርቲስታዊ የመበስበስ አደጋዎች (በአቶ መለስ ዜናዊ የተጻፈ ጥራዝ)- ጥር 1993
26. የቅንጅት ማኒፌስቶ-1997

ከላይ የተዘረዘሩት ሰነዶች በኔ እይታ በ100 ዓመት (ከ1900-2000 በነበረው) የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አድርሰዋል፡፡ እያንዳንዱን ሰነድ ልብ ብላችሁ ካያችሁት የፖለቲካ ሚናው ከፍተኛ እንደነበረ በቀላሉ መረዳት ትችላላችሁ፡፡ ለምሳሌ አቶ መለስ “ቦናፓርቲዝም” በሚል ርዕስ የጻፉት ጽሑፍ በ1993-95 የነበረውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ በከፍተኛ ጡዘት ውስጥ የጨመረ ነው፡፡ እነ ስዬ አብርሃን ከማባረር ጀምሮ የክልሎችን አስተዳደራዊ መዋቅር እስከመቀየር እና የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ለመሳሰሉት ፐሮግራሞች ትግበራ ጥርጊያ ጎዳና ያመቻቸ ነው (የጸረ-ሙስና ኮሚሽንም የርሱ ውልድ ነው)፡፡ የህዝብ ድርጅት ጽ/ቤት ማቋቋሚያ አዋጅም “ቀበሌ” የሚለውን የአስተዳደር አከፋፈል ከማስተዋወቅ ጀምሮ በቀይ ሽብር ውስጥ ከፍተኛ ሚና የነበራቸውን የጥበቃ ጓዶች እስከ ማስታጠቅ ድረስ ላሉት ታላላቅ ክስተቶች መፈጠር እንደ እርሾ ሆኖ አገልግሏል፡፡

በናንተ በኩል በዚህ ዝርዝር ውስጥ መካተት አለባቸው የምትሏቸው ሰነዶች የትኞቹ ናቸው? በናንተ ሚዛን ፖለቲካዊ ሚናቸው ሀይለኛ የሆኑትን መጠቆምና በኔ ያቀረብኩትን ዝርዝር መተቸት ትችላላችሁ (የኤርትራ ሰነዶች በዚህ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ተጽእኖ ስለነበራቸው ነው)፡፡
ሰላም
———————–
አፈንዲ ሙተቂ
ግንቦት 4/200

 

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop