February 27, 2023
3 mins read

ሕዝብ እዳው የኛ ነው!

Eskinder Nega 1 2የእንጦስን መመነን በታሪክ የማውቀው፣
በእስክንድር ነጋ ዘንድ አጅግ ደምቆ ሳየው፣
በምን ቋንቋ ጥፌ እንዴትስ ልግለጠው፣
አጥሮኝ የምያውቅ ቃል ዛሬ እያጠረኝ ነው፡፡

እንጦስ ድሎት ትቶ ገዳም የመነነው፣
ዓለምን ታዝቦ ለራስ ንስሃ ነው፡፡

ቅምጥሉ እስክንድር ምነና የሄደው፣
የሕዝብን አበሳ መከራ ሊገፍ ነው፡፡

እንደ ኢዮብ ጽናትን ክንብንብ ያረገው፣
እንደ ጴጥሮስ አለት አርጎ የፈጠረው፣
እንደ እስጢፋኖስም ብሩህ ያደረገው፣
በዚህ በእኛ ዘመን እስክንድር ነጋን ነው፡፡

ስንቱ እባብ ሰይጣንን አምኖ ሲከተለው፣
ሰባኪን በሥራው መዝኑ ሲልም ያስተማረው፣
አምላክ የመረጠው እስክንድር ነጋ ነው፡፡

በእስር ቤት ምስሉ ብር የሰበሰበው፣
አዳራሽ ውስጥ ሞልቶ ተጎንህ ነን ያለው፣
ጓደኛ ትግል አጋር ሲለው የነበረው፣
ዶሮ አንዴ እንኳን ሳይጮህ ደጋግሞ ሲከዳው፣
ተይሁዳ ብሶም አቃጥሮ ሲሰጠው፣
ተእምነት ተማተቡ ዝንፍ እንኳ እማይለው፣
ቃሎች የማይገልጡት እስክንድር ነጋ ነው፡፡

እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ስንቱ እሚያሳድደው፣
ፌስታል ያዥ እያለ ከብቱ የሚሰድበው፣
በዚህ ክፉ ዘመን የተመረጠው ሰው፣
አምነን እንቀበል እስክንድር ነጋን ነው፡፡

ጳውሎስ በእምነት ፀንቶ በምድር የታገለው፣
አንደ እስክንድር ነጋ ሲከሰስ ሲታሰር ሲፈታ የኖረው፣
ለሰላሳ አራት አመት ታሪክ እንደሚለው፡፡

ጳውሎስና ጴጥሮስ በተፈጥሮ ሰዎች የነበሩ ናቸው፣
ዛሬ የሚኖሩት ከአጥናፍ አጥናፍ ገዝፈው፣
ይህችን አላፊ ዓለም ከልባቸው ንቀው፣
አንገት ስለሰጡ በእምነታቸው ጸንተው፣
ዝንፍ ስላላሉ ጓደኛ ተከታይ በጥቅም ቢከዳቸው፡፡

በጳውሎስ በጴጥሮስ የተፈጸመውን አሕዛብ እንዳይደግመው፡፡
ሴቷ መቀነቷን ወንዱ ቀበቶውን አጥብቆ ይሰረው::

ህፀፅ ነው ህፀፅ ነው ህዝብ ሆይ ህፀፅ ነው፣
ዝም ብሎ መቀመጥ ጻድቅን እርጉም ሲያስረው፣
እርሱስ ይችለዋል ሕዝብ እዳው የኛ ነው፡፡

በላይነህ አባተ ([email protected])
የካቲት ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop