January 22, 2023
3 mins read

የሐገርን ኢኮኖሚ እየገደለ ያለው አዲሱ የብሄራዊ ባንክ ገዢ – ሳሙኤል ብዙነህ

ጎረምሳው ለአራት አመታት ይህል የጠቅላዩ የኢኮኖሚ አማካሪ ሆኖ ሰርቷል፤በውጤቱ ግሽበቱ ሰማይ ነክቷል እነ ቴሌ ተገዳዳሪ እንዲገባባቸው ተደርጓል ቴሌ ራሱም ጆሮ ግንዱ እንዲባል ተወስኗል የውጭ ባንኮች እንዲገቡ ድግሱ ተጠናቋል….
324248100 879366923114671 54310253684030286 nጎረምሳው በጠቅላዩ ቢሮ ከአዝማቾቹ የተሰጠውን ሚሽን አጠናቆ በመቶ ቢሊየን ካፒታል ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሚባል ተቋም ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆኖ ላለፉት አስራ ሁለት ወራት ሲሰራ ከርሟል፤ተቋሙ የመንግስት የልማት ተቋማትን በአንድ ላይ ሰብስቦ ለችብቸባ ማዘጋጀት እንደሆነ ውስጥ ውስጡን ይወራል….
ሰሞኑን ጎረምሳው በሚመራው ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ሶስት መቶ ሃምሳ ሺህ ኩንታል ስንዴ በሰላሳ ቀናት ውስጥ ወደ ኬኒያ ኤክስፖርት ማድረግ አለበት ተብሎ በጎረምሳው በተሰጠ ቀጭን ትዕዛዝ የኮርፖሬሽኑ ባለስልጣናት ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ላይ ናቸው፤ገበሬው በኩንታል ለዮኒየኖች በ3200 እንዲያቀርብ ዩኒየኖች ደግሞ ለኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን በ3378 እንዲያቀርቡ አስገዳጅ ተመን ቢቀመጥም ገበሬው አያዋጣኝም ብሎ ምርቱን አፍኖ ይዟል….
ገበሬው ምርቱን በለሊት እያወጣ ያዋጣኛል ባለው ዋጋ መሸጥን ምርጫው አድርጓል፤ስንዴም ወግ ደርሷት በኮንትሮባንድነት ተሰይማ ኬላ ተበጅቶላታል….ጎረምሳው ወደ ኬኒያ የሚላከው ሶስት መቶ ሃምሳ ሺህ ኩንታል ስንዴ ካልተሳካ እዚህ ወንበር ላይ አትቆዩም እያለ በንግድ ስራ ኮርፖሬሽን ሃላፊዎች ላይ መዛት ከጀመረ ሰነብብቷል፤ኮርፖሬሽኑ እስከ አሁን የገዛውና ወደ መጋዛኑ ያስገባው ሃያ ሺህ ኩንታል ገደማ ነው….የኮርፖሬሽኑ ሃላፊዎች መስሪያ ቤታቸውን ለኪሳራ የሚዳርግ ስራ መሆኑን በኬኒያ የአንድ ቶን የስንዴ ዋጋን ጠቅሰው ቢከራከሩም ላኩ ላኩ አያገባችሁም ተብለዋል፤ዋናው የሚፈለገው ኢትዮጵያ ስንዴ ወደ ኬኒያ ላከች የሚለውን ዜና መስራት ነው ……..
ጎረምሳው ዛሬ የብሄራዊ ባንክ ገዢ ሆኗል ተብለናል፤አዝማቾቹ የብርና የዶላር ምጣኔ አሁንም ልክ አይደለም መስተካከል አለበት የሚሉ ናቸው….ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ አንድ የአሜሪካን ዶላር በሁሉም የንግድ ባንኮች ከዛሬ ጀምሮ በመቶ አስር ብር ይመነዛራል ተብሎ ቢነገርህ እንዳትበረግግ
ሳሙኤል ብዙነህ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop