ሚ/ር ብርሃኑ ሰማሁት እንደሌላው ኢትዮጵያዊ በሚዲያ ነው…!

በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የክስ መዝገብ የተጠቀሱትን አቶ ስብሃት ነጋ እና የተወሰኑ ሰዎች መፈታታቸውን በተመለከተ በኢዜማ ብሄራዊ ስራ አስፈፃሚ የአስቸኳይ ስብሰባ ላይ የፓርቲው መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ መጀመሪያ የተጠየቁት በሚንስትሮች ም/ቤት ጉዳዩ ቀርቦ እንደሆነ መረጃ እንዲሰጡ ነው።
በሰጡት መልስ ጉዳዩ በሚንስተሮች ም/ቤት እንዳልቀረበ እና እንደ ማንኛችንም በሚድያ እንደሰሙ ነው ። ለነገሩ ጠ/ሚንስትሩም ይህን (እሳቸውም እንዳልሰሙ) አረጋግጠዋል (የጉድ ሀገር!)
የኢዜማም መግለጫ የሚጠቁመው አቋሙን ነው። ከዚህ እውነት በወጣ መልኩ ኢዜማ ላይ ማላዘንና ሴራ መጎንጎን ትርጉም አልባ ነው ። የሚገኝ ጥቅምም የለውም ።[ ተክሌ በቀለ ]
ተጨማሪ ያንብቡ:  የሰሜኑ ጦርነት እና ድርድር|Prosperity | Amhara |Fano | Tigray | Abiy Ahmed|

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share