January 9, 2022
5 mins read

ወደ ይህ አድግ ሰዎች ሆይ! – በላይነህ አባተ

በጭራቆች ተጨፍጭፈው በሞቱት ሰማእታት ሥም ይቅርታ ተቀባይና ምህረት አድራጊ እንድትሆኑ ማን ቀባችሁ?

በላይነህ አባተ ([email protected])

abiy ahmed in mekelle 300x170 1ይህ አድግ ቁጥር ሁለት ሳይመጣ “የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ነን፣ የነፃነት ጋዜጠኞች ነን፣ ተቀዋሚ ድርጅት ነን፣ የህግ ባለሙያ ነን፣ የኢኮኖሚ ጠበብት ነን  ወዘተርፈ” ሲሉ ኖረው ከአራት ዓመታት ወዲህ “የሙሴና ኢያሱ” ተከታይ ብቻ ሳይሆን አምላኪዎች ሆነው አረፉ፡፡

እነዚህ ጉደኞች “ የይህ አድግ ቁጥር ሁለት መሪዎች ይቅርታ ስለጠየቁና ኢትዮጵያን ከፍ ከፍ አድርገው ስለተናገሩ ምህረት በማድረግ ደግፈን ተክተልናቸው ነበር” እያሉ ጅብ የመሰሉ አድጎች በመንጋጋችቸውና በምግጭላቸው ግጠው በፈጠሩት የሕዝብ ቁስል ላይ ስንጥር እንጨት እየሰደዱ ይገኛሉ፡፡

የሙሴዎችና የኢያሱዎች ተከታይ “ወደ ይህ አድግ ሰዎች ሆይ?”

ባለፉት ሰላሳ አመታት ውስጥ በጋምቤላ፣ በኦጋዴን፣ በአምቦ፣ በአዋሳና አማራ በሚኖርበት በማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል በአገዛዙ ታጣቂዎች እንደታጨደ፣ በወህኒ ተገርፎና ተጠብሶ አንዳለቀ፣ እንደመከነና ሲሰደድም የጅብ እራት ሆኖ እንደቀረ ታውቃላችሁ፡፡

እና በዚህ ለሰላሳ ዓመታት በተጨፈጨው ሕዝብ ሥም ይቅርታ ተጠያቂና ምህረት ሰጪ አድርጎ እናንተን ወደ ይህ አድግ ሰዎችን ማን ሾማችሁ? እግዚአብሔር በመንፈስ ታይቶ ተወካይ አደረጋችሁ ወይስ ሰማእታት ከመጨፍጨፋቸው በፊት ለጨፈጨፏቸው አረመኔ ጭራቆች ምህረት እንድታደርጉ ፊርማ ትተውላችሁ አለፉ?

ዓይናችሁን እንደ ወፈጥ አፍጣችሁ በሰማእታት ሥም ምህረት አድርገናል ስትሉ ህሊናችሁን የጉንዳን ያህል  እንኳን አይቆነጥጣችሁም ወይ? እንኳን እናንተን ዓይነ ፈጣጣዎችን ቋሚ የሙታን ልጆች ወይም ወላጆችስ ይቅርታ እንዲያደረጉ ቃላቸውን ባልሰጧቸው የጭራቆች ሰለባዎች ሥም ምህረት የማድረግ መብት አላቸው ወይ?

ጭራቆቹን ሲታገል በአንቦ፣ በጎንደር፣ በባህርዳር፣ በዳንግላ፣ በወልዲያ፣ በአዲስ አበባ ወዘተርፈ  በአረመኔ ባሩድ የተበረቀሰው ወጣት ጭንቅላት የእናንተ ጭንቅላት ነወይ? በአረመኔዎች ላይ ስታምጥ የተበሳው የሽብሬ ደረት የእናንተ ደረት ነወይ? በኦጋዴን እሬሳው የተጎተተው ጎበዝ ገላ የእናንተ ሬሳ ነውይ? ወለጋ እናቱ እንዲቀመጡበት የታዘዙት አስከሬን የእናንተ ነወይ? በጋምቤላ በመደዳ የተረፈረፈው የሬሳ ክምር የእናንተ ነወይ? የእናንተ ታልሆን እንደ ዝንብ ወተት ጥልቅ ብላቸሁ ይቅርታ ተጠያቂና ምህረት ሰጪ ያደረጋችሁ ማን ነው?

ናዚዎች ዛሬ እንኳን በዘጠናና በመቶ ዘመናቸው በዓለም ላይ እየተለቀሙ ለፍርድ በሚቀርቡበት ሰዓት ምነው እናንተ በክቡሩ የሰው ነፍስ እየቀለዳችሁ በሌላ ሰው ነፍስ ራሳችሁን ይቅርታ ተጠያቂና ምህረት አድራጊ ሾማችሁ ድግሷ እንዳማረላት ወይዘሮ ቂጣችሁን ወዲያ ወዲህ ተማማታት አልቆጠብ አላችሁ?

ወደ ይህ አድግ ሰዎች ሆይ! ፍትህ የሌለው እርቅና ሥራ የሌለው እምነት የሞተ መሆኑን መገንዘብ ምነው ተሳናችሁ? ፍትህን እንጦሮጦስ በመወርወር በሰማእታት ነፍስ ይቅርታ ተቀባይና ምህረት አድራጊ እንድትሆኑ ማን ቀባችሁ?

ጥር  ሁለት ሺ አስራ አራት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

January 18, 2025
በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop