ወደ ይህ አድግ ሰዎች ሆይ! – በላይነህ አባተ

በጭራቆች ተጨፍጭፈው በሞቱት ሰማእታት ሥም ይቅርታ ተቀባይና ምህረት አድራጊ እንድትሆኑ ማን ቀባችሁ?

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ይህ አድግ ቁጥር ሁለት ሳይመጣ “የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ነን፣ የነፃነት ጋዜጠኞች ነን፣ ተቀዋሚ ድርጅት ነን፣ የህግ ባለሙያ ነን፣ የኢኮኖሚ ጠበብት ነን  ወዘተርፈ” ሲሉ ኖረው ከአራት ዓመታት ወዲህ “የሙሴና ኢያሱ” ተከታይ ብቻ ሳይሆን አምላኪዎች ሆነው አረፉ፡፡

እነዚህ ጉደኞች “ የይህ አድግ ቁጥር ሁለት መሪዎች ይቅርታ ስለጠየቁና ኢትዮጵያን ከፍ ከፍ አድርገው ስለተናገሩ ምህረት በማድረግ ደግፈን ተክተልናቸው ነበር” እያሉ ጅብ የመሰሉ አድጎች በመንጋጋችቸውና በምግጭላቸው ግጠው በፈጠሩት የሕዝብ ቁስል ላይ ስንጥር እንጨት እየሰደዱ ይገኛሉ፡፡

የሙሴዎችና የኢያሱዎች ተከታይ “ወደ ይህ አድግ ሰዎች ሆይ?”

ባለፉት ሰላሳ አመታት ውስጥ በጋምቤላ፣ በኦጋዴን፣ በአምቦ፣ በአዋሳና አማራ በሚኖርበት በማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል በአገዛዙ ታጣቂዎች እንደታጨደ፣ በወህኒ ተገርፎና ተጠብሶ አንዳለቀ፣ እንደመከነና ሲሰደድም የጅብ እራት ሆኖ እንደቀረ ታውቃላችሁ፡፡

እና በዚህ ለሰላሳ ዓመታት በተጨፈጨው ሕዝብ ሥም ይቅርታ ተጠያቂና ምህረት ሰጪ አድርጎ እናንተን ወደ ይህ አድግ ሰዎችን ማን ሾማችሁ? እግዚአብሔር በመንፈስ ታይቶ ተወካይ አደረጋችሁ ወይስ ሰማእታት ከመጨፍጨፋቸው በፊት ለጨፈጨፏቸው አረመኔ ጭራቆች ምህረት እንድታደርጉ ፊርማ ትተውላችሁ አለፉ?

ዓይናችሁን እንደ ወፈጥ አፍጣችሁ በሰማእታት ሥም ምህረት አድርገናል ስትሉ ህሊናችሁን የጉንዳን ያህል  እንኳን አይቆነጥጣችሁም ወይ? እንኳን እናንተን ዓይነ ፈጣጣዎችን ቋሚ የሙታን ልጆች ወይም ወላጆችስ ይቅርታ እንዲያደረጉ ቃላቸውን ባልሰጧቸው የጭራቆች ሰለባዎች ሥም ምህረት የማድረግ መብት አላቸው ወይ?

ጭራቆቹን ሲታገል በአንቦ፣ በጎንደር፣ በባህርዳር፣ በዳንግላ፣ በወልዲያ፣ በአዲስ አበባ ወዘተርፈ  በአረመኔ ባሩድ የተበረቀሰው ወጣት ጭንቅላት የእናንተ ጭንቅላት ነወይ? በአረመኔዎች ላይ ስታምጥ የተበሳው የሽብሬ ደረት የእናንተ ደረት ነወይ? በኦጋዴን እሬሳው የተጎተተው ጎበዝ ገላ የእናንተ ሬሳ ነውይ? ወለጋ እናቱ እንዲቀመጡበት የታዘዙት አስከሬን የእናንተ ነወይ? በጋምቤላ በመደዳ የተረፈረፈው የሬሳ ክምር የእናንተ ነወይ? የእናንተ ታልሆን እንደ ዝንብ ወተት ጥልቅ ብላቸሁ ይቅርታ ተጠያቂና ምህረት ሰጪ ያደረጋችሁ ማን ነው?

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባላት የመልቀቂያ ደብዳቤ

ናዚዎች ዛሬ እንኳን በዘጠናና በመቶ ዘመናቸው በዓለም ላይ እየተለቀሙ ለፍርድ በሚቀርቡበት ሰዓት ምነው እናንተ በክቡሩ የሰው ነፍስ እየቀለዳችሁ በሌላ ሰው ነፍስ ራሳችሁን ይቅርታ ተጠያቂና ምህረት አድራጊ ሾማችሁ ድግሷ እንዳማረላት ወይዘሮ ቂጣችሁን ወዲያ ወዲህ ተማማታት አልቆጠብ አላችሁ?

ወደ ይህ አድግ ሰዎች ሆይ! ፍትህ የሌለው እርቅና ሥራ የሌለው እምነት የሞተ መሆኑን መገንዘብ ምነው ተሳናችሁ? ፍትህን እንጦሮጦስ በመወርወር በሰማእታት ነፍስ ይቅርታ ተቀባይና ምህረት አድራጊ እንድትሆኑ ማን ቀባችሁ?

ጥር  ሁለት ሺ አስራ አራት ዓ.ም.

4 Comments

  1. “በጭራቆች ተጨፍጭፈው በሞቱት ሰማእታት ሥም ይቅርታ ተቀባይና ምህረት አድራጊ እንድትሆኑ ማን ቀባችሁ?”
    በሞቱት ሰማእታት ሥም ይቅርታ እና ምሕረት ተደረገ ስትል የሞቱትን ማቃለል አይሆንብህም?
    ብዙዎቻችን በጠ/ሚሩ አስተዳደር ውሳኔ አልተስማማንም። ጠ/ሚሩ እያስተላለፉ ያለውን ማብራሪያ በጥሞና እየተከታተልን ነው።
    ማንኛችንም ብንሆን አገር ወዳድ እስከ ሆንን ድረስ ለትህነግ የሚመቻች ሁኔታ እንዲፈጠር ምክን ያት መሆን አንሻም።
    አንተ ግ ን ሳየው በስድብ ናዳ በጥላቻ እየተናጥክ ነው። ምክን ያታዊ ለመሆን ትንሽ ብትሞክር ይበጃልና አስብበት!

    • Ato Alem,

      You said “ማንኛችንም ብንሆን C እስከ ሆንን ድረስ ለትህነግ የሚመቻች ሁኔታ እንዲፈጠር ምክን ያት መሆን አንሻም።” How is demanding justice for people massacred by TPLF making TPLF uncomfortable. How does killing justice for massacred people by TPLF make TPLF comfortable? What is ” አገር ወዳድ” while you are denying justice your fellow citizens massacred when they demand freedom for you?
      Are you thinking with your brain or spinal cord?

      You are terribly unprincipled person. As long as it makes TPLF uncomfortable, you will do anything evil including denying justice for the miscreed people. Shame!!!!

  2. ሰውየው የሲአይኤ ምልምል ነው። ለጊዜው የአፍሪካ መሪ መስሎ እንዲተውን የሰጡትን ድራማ ፈቃድ ገልብጠው ቀጭን ትእዛዝ ጌቶቹ ሲሰጡት ክው ብሎ ደነገጠ። ከወያኔ የተሻለ አሽከር መሆን ይጠበቅበታል። ሕሊና ያለው ፍጡር ከሆነ ግን፥ ቢያንስ ቢያንስ የሚታረዱትን፣ የሚሳደዱትን ንጹሐን ሰዎች ይድረስላቸው። ካልቻለ ደግሞ ይውረድ። ከሰዎች ፍርድ ቢያመልጥ እንኳ፥ ከእግዚአብሔር ፍርድ እንዴት ሊያመልጥ ይችላል? ፈጣሪ ፈጣሪ የሚለው የድራማው አካል ካልሆነና ከልቡ አምኖበት ከሆነ። ሰውን ማታለል ይቻል ይሆናል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share