“ድንገት አመሻሹ ላይ ነው ዕቃችሁን ይዛችሁ ውጡ የተባልነው” የባልደራስ አመራር

የባልደራስ ከፍተኛ አመራር የሆኑትና በቂሊንጦ ከአቶ እስክንድር ነጋ ጋር ታስረው የነበሩት የፓርቲው የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ቸኮል በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 12፡30 አካባቢ የማረሚያ ቤቱ ሠራተኞች ድንገት መጥተው ከማረሚያ ቤቱ እንዲወጡ እንደነገሯቸው አስስረድተዋል።

“ድንገት አመሻሽ ላይ መጥተው ዕቃችሁን ይዛችሁ ውጡ አሉን፤ ያው እቃችንን ይዘን ወጣን። ምንም የምናውቀው ነገር የለም” በማለት አቶ ስንታየሁ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንደወጡ በስልክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።  አቶ ስንታየሁን በስልክ ባገኘበት ወቅት ከቂሊንጦ ማረሚያ ወጥተው ከአቶ እስክንድር ጋር ከማረሚያ ቤቱ አቅራቢያ ወደሚገኝ ቤተ ክርስቲያን እያመሩ እንደሆነም ገልጸዋል። “በዋናነት የተፈታነው በአምላክ ኃይል ነው፤ እውነት ነው ያሸነፈው፤ የሕዝብ ትግል፣ የሕዝብ እንባ ነው ያሸነፈው” ብለዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በፓርላማ ጥያቄ ያስነሳው የትግራይ እና ወልቃይት በጀት ድልድል ጉዳይ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share