ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ታላቁን የድል ዜና መቀሌ ላይ ሆነን እናበስራለን አሉ

የመከላከያ ሰራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሕወሓት ሽብር ቡድንን እስከ መጨረሻው በመቅበር ታላቁን የድል ዜና መቀሌ ላይ ሆነን እናበስራለን አሉ።
የልዩ ዘመቻዎች ኃይል፣ የሪፐብሊክ ጥበቃ ኃይል እና የአየር ወለድ አባላት በጭንቅ ላይ ያለች አገርን ችግር የፈቱ የጭንቅ ቀን ደራሾች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ሌተናል ጄኔራሉ ይህንን የተናገሩት የመጀመሪያው ምዕራፍ የሽብር ቡድኑን የመደምሰስ ግዳጅ በድል መገባደድ እና ለቀጣይ ወሳኝ ተልዕኮ መነቃቃትን ለመፍጠር በሚያስችል መልኩ በግንባር በተካሄደ መድረክ ላይ ተገኝተው ነው።
ቀይ መለዮ ለባሾቹ በወሳኝ ወቅት አስቸጋሪና ፈታኝ ግዳጆችን በድል በመወጣት በደማቅ ቀለም የተፃፈ ታሪክ መስራታቸውን ተናግረዋል።
ጀግኖቹ ከሰሞኑ በጣርማበርና ዙሪያገባዎቹ የፈፀሙት አንፀባራቂ ድል የጠላትን ቅስም የሰበረ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ባጫ አሁንም የደም የመስዋዕትነት እና የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን ቀይ መለዮዋቸውን አጥልቀው ለዳግም ድል መትጋት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የልዩ ዘመቻዎች፣ የሪፐብሊኩ ኃይልና አየር ወለዶች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች እና የምድር ላይ ድሮን መሆናቸውን እንዳስመሰከሩ ሁሉ የኅልውናችን ጠንቅ ሆኖ በአንዳንድ ፅንፈኛ ምዕራባዊያን የሚጋለበውን የሕወሓት ሽብር ቡድን እስከ መጨረሻው በመቅበር ታላቁን የድል ዜና መቀሌ ላይ ሆነን እናበስራለን ብለዋል።
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦
የአማርኛ ፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ ይከተሉ
ኅዳር 30/2014 (ዋልታ)
ተጨማሪ ያንብቡ:  የሕብር ሬዲዮ ሚያዚያ 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ፕሮግራም

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share