የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከግምባር ያስተላለፉት መልዕክት

  • ዋናው ጉዳይ ጠላት ተሸንፏል፤ ጠላት መበተን ፣ ጠላት መደምስስ ነው ቀሪ ስራችን፤ ጠላትን በትነን በጋራ የምናይበት ዕቅድን ጨርሰናል፣
  •  አሁን ያለንበት ቦታ የአንድ ወታደር ምሽግ ነው፣ በእኛ ጦርና በጠላት ጦር መካከል ያለ ክፍት ቦታ በጋራ የተያዘ ነው፤
  • አሁን የገጠመን ጠላት የሚዘርፍ የሚገድል፣ የሚደፍር፣ ለራሱ ክብር የሌለው ለሀገር ክብር የሌለው፣ ለሴቶች ክብር የሌለው ፣ እራሱን አዋርዶ እኛንም ለማዋረድ የፈለገ ነው፣
  • ይህንን ለማድረግ ታውሮ ገብቷል፣ ሳያልም ሳያቅድ በእውር ድንብር ገብቷል፣ በእውር ድንብር ግን መውጣት አይችልም፣
  •  በምስራቅ ያሳከነውን አመርቂ ድል እንደግማለን፤ በእውር ድንብር የገባው ጠላት ተኩሱ እንዳይወጣ፣ የዘረፈውን ይዞ እንዳይወጣ ይደመሰሳል፣
  • ይህንን ለመፈጸም እድቅ አልቋል፣ ሰራዊቱ ዝግጁ ነው፣ አመራሩ ዝግጁ ነው፣ ድል ከፊታችን ነው
ተጨማሪ ያንብቡ:   አብይ አህመድ ኦሮሚያ ለምን ተነካች ባዲስ አበባ ብለው ለምን ደነፋ ?!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share