November 19, 2021
2 mins read

በወረኢሉ ፣ አጣዬ ፣ ጭፍራ እና ቡርካ ግንባሮች በተካሄዱ ውጊያዎች በርካታ የሽብር ኃይሉ ተዋጊዎች ሲደመሰሱ

258835701 1681806528661001 5598355288573307255 n ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኃይል ቁስለኛና ምርኮኛ ሆኗል፡፡
ሕዳር 10/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል አባላት ለወረራ በተንቀሳቀሱባቸው የአማራና አፋር አካባቢዎች በርካታ አረመኔያዊ ግፍና በደል መፈፀማቸውን አጋልጠዋል፡፡

የመከላከያ ሠራዊቱንና ሌሎች የጸጥታ ኃይሎችን ምት መቋቋም ተስኗቸው የተማረኩት እነዚህ የአሸባሪው አባላት አጎራባቾቻቸው ያሉትን የአማራና የአፋር ሕዝብ ለማጥፋት ከሽብር ቡድኑ መሪዎች ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው መግለጻቸውን ከመከላከያ ሠራዊት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
በኢፌዴሪ አየር ሃይል በቅርቡ ጥቃት በተፈፀመባቸው አግበ ፣ አጉላዕ ፣ ኩሃ እና እዳጋ ሃሙስ በተሰኙ ወታደራዊ ማሰልጠኛዎች በተሰጣቸው የአጭር ጊዜ ስልጠና ለግዳጅ መሰማራታቸውን ምርኮኞቹ ገልጸዋል፡፡
በከሃዲዎቹ ብርጋዴር ጄኔራል አብርሃ ድንኩል፣ ኮሎኔል ዋልታ መኮንን፣ ኮሎኔል አፈራ አሰፋ እና ሌሎች የሽብርተኛው ወታደራዊ ክንፍ አመራሮች እየታዘዙ እስከ ተንታ፣ ወረኢሉ እና አጣዬ ሾልከው በመግባት ሕዝቡን በማፈናቀል፣ ወጣቶችን በአሰቃቂ ሁኔታ በመረሸን፣ ሴቶችን በመድፈር፣ ንብረት በመዝረፍና በማውደም በርካታ አፀያፊ ተግባራትን መፈፀማቸውን በመከላከያ ሠራዊት የተማረኩት አባላት አረጋግጠዋል፡፡
ወራሪውን ጠላት ደምስስ!
የጀግንነት ታሪክህን ዳግም አድስ!
ያለ መስዋእትነት ድል አይገኝም!
ነፃነትህን አትስጥ!
ተዋርዶ ከመኖር በክብር መሞት ይሻላል!
አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
259086039 1681806621994325 2467282050371399089 n 257808184 1681805935327727 5638616571027027642 n 258750436 1681806741994313 2808059368888305613 n

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop