የኬንያው ፕሬዝዳንት ምዕራባዊያን መገናኛ ብዙኃንን መመልከት ያቆሙበትን ምክንያት ገለፁ

የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የምዕራባዊያን መገናኛ ብዙኃንን ዜናዎችን መመልከት ያቆሙበትን ምክንያት ገለፁ፡፡
ምዕራባዊያን መገናኛ ብዙኃንን በአፍሪካ ጉዳይ ላይ ዘገባ ሲሰሩ በቦታው ከመገኘት ይልቅ በርቀት ሆኖ መስራትን ይመርጣሉ ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ በርካታ የምዕራባዊያን አገራት ዜጎች በተገኙበት መድረክ ያደረጉት ንግግር ‹‹ቱናቸኪ›› (2nacheck) በሚሰኝ እና በስዋህሊ ቋንቋ ‹‹እየተመለከትን ነው›› በሚል ትርጉም የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክትና በአኅጉሪቱ ላይ ያለውን የምዕራባዊን የተዛባ እሳቤ ለመግለጥ በተመሰረተው ተነሳሽነት ላይ ለተመልካቾች ወጥቷል፡፡
የምዕራባዊያን መገናኛ ብዙኃን በአፍሪካ ላይ የሚሰሩትን የተዛባ ዘገባ እንዲቆሙ በተደጋጋሚ ሲጠይቁ የሚደመጡት ኡሁሩ ‹‹በቢግ ፎር አጀንዳ ኬንያ›› ላይ ባደረጉት ንግግር የመገናኛ ብዙኃኑን ፈር የለቀቀ አካሄድ ኮንነዋል፡፡
‹‹እነ አልጀዚራ፣ ሲኤንኤን፣ ስካይኒውስ፣ ቢቢሲ እና ሌሎችም በርዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ ላይ የተፈጠረን ነገር እንዳንዴም የአፍሪካ የምዕራብ አቅጣጫ ጠርዝ በምትገኘው ናይጀሪያ ሆነው ዘግበው ሲጨርሱ ‹ለዘገባው ጆን ኋይት ከናይሮቢ ኬንያ› ይላል ሲሉ ነው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ የተቹት፡፡ ይህም ሁሉም የሚያውቀውን ክዶ የሽብር ቡድኑ ቦኮሃራም ኬንያ ነው የሚኖረው እንደማለት ነው ብለዋል፡፡
አፍሪካዊያን አንድ ቢሆኑም በየራሳቸው ልዩ የሆኑ አገራት በመሆናቸው የምዕራባዊያን መገናኛ ብዙኃን ይህንኑ በማክበር የሚዘግቡት ዘገባ በቦታውና በሰዓቱ በመገኘት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
ኅዳር 8/2014 (ዋልታ)
ተጨማሪ ያንብቡ:  የጨነቀው መከላከያ ከባህርዳር የተሠማው|ከዳባት የድል ዜና ፣ እንጅባራ ሰበር|ጎንደር የመንግስት ሃይሎች አሳዛ'ኝ ዜና

2 Comments

  1. The so called big country America, state department a higher official but he is doing silly thing in the ground, day and night working to dismantle the unity of Ethiopia and accomplish the vision of Egypt and also bring to power the terrorist group. If anybody or country is against their interest, they vow first to sat “Terrorist”, one day you will be liable on International Criminal Court if Truth Prevails.
    Ever body you see how this bullshit US foreign policy play the game in the world and intervene deliberately in the sovereignty of one country.
    Long live to Ethiopia!!

  2. The so called big country America, state department a higher official but he is doing silly thing in the ground, day and night working to dismantle the unity of Ethiopia and accomplish the vision of Egypt and also bring to power the terrorist group. If anybody or country is against their interest, they vow first to say “Terrorist”, one day you will be liable on International Criminal Court if Truth Prevails.
    Ever body you see how this bullshit US foreign policy play the game in the world and intervene deliberately in the sovereignty of one country.
    Long live to Ethiopia!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share