የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ዛሬ እሁድ በትግራይ ክልል «ማይጠምሪ» እና « አድዋ » አካባቢ የሚገኙ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ግንባር (ሕወሓት) ወታደራዊ ይዞታዎችን በአየር ማጥቃቱን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎት ዐስታወቀ። የጦር ኃይሉ ዛሬ ረፋዱን «በማይጠምሪ የሚገኝ የወታደራዊ ማሰልጠኛ እና የሰው ኃይል ማደራጃ ይዞታዎች በአየር ተመቷል» ብሏል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ማይጠብሪ የሚገኘውን የአሸባሪውን ሕወሓት ማዕከል መታ
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቀጥሎ ባወጣው መግለጫው ደግሞ «ዐድዋ አካባቢ የሚገኘው፣ የጠላት ወታደራዊ ትጥቅ እና ወታደራዊ አልባሳትን አመሳስሎ የሚያመርትበት ማዕከል በአየር ድብደባ ከጥቅም ውጭ ሆኗል።» ብሏል።በማይጠምሪ በሚገኘው የወታደራዊ ማሰልጠኛ እና የከባድ ጦር መሣርያዎች ማከማቻ ላይ የተሳካ የአየር ጥቃት መወሰዱን ላረጋጋጥላችሁ እችላለሁ ።» ሲሉ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትሩ ለገሰ ቱሉ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል።
የህወሃት ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ የጥቃቱን መፈጸም ለሮይተርስ አረጋግጠዋል። «ጥቃቱ በአንድ የገጠር ሆስፒታል አቅራቢያ ተፈጽሟል።» ብለዋል። በዐድዋ በተፈጸመው ጥቃት «ቀደም ሲል በኢትዮጵያ እና የኤርትራ ወታደሮች ውድመት ደርሶበት የነበረው እና ጥቂት ተርፎ የነበረው የአልሜዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ መመታቱን » በቲውተር ባሰፈሩት መልዕክት አረጋግጠዋል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያን ስደተኞች የሚገኙባቸው የማይ አኒ እና አዲ ሃሩሽ የመጠለያ ጣብያዎች በማይጠምሪ አቅራቢያ ይገኛሉ። እንደ ኮሚኒኬሽን ሚንስትሩ ለገሰ ቱሉ የመጠለያ ጣብያዎቹ ለአየር ጥቃቱ ተጋላጭ እንዳልነበሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር እና የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ኮሚሽነር የመጠለያ ጣብያዎቹን ደህንነት በተመለከተ ላቀረበላቸው ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ እንዳልሰጡ ሮይተርስ የዜና ምንጩ ጠቅሷል።
DW
የእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ admin@zehabesha.com በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!