አሜሪካ ለአማራ ክልል የምታደርገውን የሰብዓዊ ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች

 

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ እና በአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ረዳት ኀላፊ ሳራህ ቻርለስ ከአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ዛሬ ጠዋት ከአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ጋር የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
በውይይታቸውም አሸባሪው ትሕነግ ባደረሰው ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ ምን እንደሚመስል እና በቀጣይ ድጋፍ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም ተነጋግረናል ብለዋል፡፡
አምባሳደሯ በሰጡት መግለጫ መሠረት ጦርነት በሚካሄድባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ንጹኃን ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል፡፡ በጦርነት፣ በርሃብ እና አለመረጋጋት ጊዜ የሚያጋጥም ችግር ድንበር የለውም ያሉት ጊታ ፓሲ የሕዝቡን ሰቆቃ ለማስቀረት ለሚፈጠረው ቀውስ እልባት መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ያለምንም ልዩነት ድጋፍ ለማድረግ አሜሪካ ቁርጠኛ መሆኗንም አስታውቀዋል፡፡
245856903 4489496294474867 6339846383873795049 n
በአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) የሰብዓዊ ጉዳዮች ረዳት ኀላፊ ሳራህ ቻርለስ በኢትዮጵያ በጦርነቱ ምክንያት የተፈጠረው የብዙኃን ሰቆቃ አሳስቦናል በማለት ተናግረዋል፡፡ ጦርነት እየተካሄደባቸው በሚገኙ አካባቢዎች ሴቶች እና ህጻናትን ጨምሮ በርካቶች ከቀያቸው ተፈናቅለው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ተረድተናልም ነው ያሉት፡፡ የምግብ እጥረት፣ የመጠለያ ችግር፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ እና የሕክምና ችግር ማጋጠሙን ጠቅሰዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለስ እና ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል፡፡
ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ጋር በአማራ ክልል የሚሠሩ አጋሮች እንዳሏቸው ያነሱት ረዳት ኀላፊዋ ዛሬ ባሕር ዳር የተገኙት በክልሉ የሚደረገውን ድጋፍ አጠናክሮ ለመቀጠል እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡
በአማራ ክልል የተወረሩ አካባቢዎችን ጨምሮ ድርጅታቸው በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የሚደረገውን ድጋፍ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ የእኛ ሠራተኞች ከዚህ ያሉት ሕይወት የማዳን ተልዕኮ ስላለን ነው፤የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማገልገል እና ፍላጎታቸውን ለማሟላት ነው ብለዋል።
Amhara Media Corporation
ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: በኤርትራ ትግርኛ ተናጋሪ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአሰሳ ተሳተፉ በሚል ሕዝቡ ቁጣውን ገለጸ

1 Comment

  1. It is amazing seeing of that US Ambassador & their officials visit in Amhara region. If America has not been on a wrong direction of supporting terrorist & rebellion group, TPLF before, there was no chance of all those mess happened. Still they have to side on the people of Ethiopia and support government of Ethiopia to culminate the war and force TPLF leaders to be sue on international criminal court as they committed genocides, mass murder and displacement of many people. Why America doesn’t make a clear stand on this issue and proudly say spade is spade??

    Hoping you ambassador lately aware of all the sabotage that has been made in Ethiopian people, so try to pass clear message to Biden administration that America is on wrong foreign policy in Ethiopia internal affairs and instead of looking for its interest only and side criminals it is better to listen the voice and struggle of people of Ethiopia.

    Long live to Ethiopia!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share