የኢፌዲሪ አየር ኃይል በመቐለ ከተማ የሚገኙና አሸባሪ ቡድኑ ለሽብር ተግባሩ የሚጠቀምባቸውን ስፍራዎች፣ እና መሳሪያዎች ላይ ካለፈው ሰኞ ጀምሮ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። መከላከያ ሰራዊቱ በአየር ኃይሉ አማካኝነት በመቐለ ከተማ የሚገኙ የግንኙነት መሳሪያዎችን እና ታወሮችን የሽብር ቡድኑ ሲጠቀምባቸው መቆየቱን በማረጋገጥ እርምጃ የወሰደ ሲሆን ዛሬም የአስቸኳይ ጊዜ ማጣሪያ ባወጣው መረጃ የሽብር ቡድኑ ለመሳሪያ ማከማቻነት እና ለጥፋት ስራው የሚጠቀምባቸው አካባቢዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን አረጋግጧል።
በመቐለ የሚገኘው መስፍን ኢንዱስትሪያል የአሸባሪው ህወሓት የመሳሪያ ማከማቻ፣ መስሪያ እና መጠገኛ ሆኗል።
በመቐለ ከተማ የሚገኘው መስፍን ኢንዱስትሪያል የአሸባሪው ህወሓት የጦር መሳሪያ ማከማቻ፣ መስሪያ እና የከባድ መሳሪያዎች መጠገኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ታማኝ ምንጮች ነግረውናል። እንደምንጮቻችን ገለጻ አሸባሪው ቡድን በመቐለ ከተማ የሚገኘውን የመስፍን ኢንዱስትሪያልን ሙሉ በሙሉ የመሳሪያ ማከማቻ እና ማምረቻ እንዲሁም የከባድ መሳሪያዎች የጥገና ማዕከል አድርጎ እየተጠቀመበት ነው።
ምስል፡ ከድረገጽ
(ኢ ፕ ድ)
የእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ admin@zehabesha.com በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!
የተገነባው በተሰረቀ በኛው ሀብት የተገነባዉ ኢትዮጵያን ለማጥፋት መሆኑ እየታወቀ ምን አሸማቀቃችሁ? የሌቦችን ንብረት ዱቄት አድርገነዋል የኢትዮጵያ ህዝብ ደስ ይበልህ ማለት ማንን ገደለ?