የሱዳን ጦርን የሚደግፉ በሺሕዎች የሚቆጠሩ የመንግሥት ተቃዋሚዎች ዛሬ ቅዳሜ በኻርቱም አደባባይ ወጡ። በዋና ከተማዋ በሚገኘው ፕሬዝደንታዊ ጽህፈት ቤት ደጃፍ የተሰበሰቡ ተቃዋሚዎች “የረሐብ መንግሥት” ያሉት የጠቅላይ ምኒስትር አብደላ ሐምዶክ አስተዳደር ከሥልጣን እንዲለቅ ጥሪ ማቅረባቸውን ሬውተርስ ዘግቧል። የተቃውሞ ሰልፉ የቀድሞው የሱዳን መሪ ኦማር አል በሺርን ከሥልጣን ለማውረድ ያመጹ ቡድኖችን ጨምሮ ለጦሩ በሚወግኑ የነፃነት እና የለውጥ ኃይሎች ስብስብ አንድ አንጃ የተጠራ ነበር።
አስተባባሪው የትግሬ አሸባሪ ነው መቼም እግሩ በረገጠበት ሰላም የለም