ህዳሴ ግድብን ለማደናቀፍ ማሰብ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ እንደማይደራደሩ ካለመረዳት የሚመነጭ ነው – ሌ/ጄ አስራት ዴኔሮ

የምድር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል አስራት ዴኔሮ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ታላቁ የህዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፣ ለፕሮጀክቱ መሳካት እየተከናወነ ያለውን እረፍት አልባ የሰራዊቱ የግዳጅ አፈፃፀም አድንቀዋል፤ ምስጋናም አቅርበዋል።
ጄነራል መኮንኑ በጉብኝቱ ወቅት የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ለማደናቀፍ ማሰብ ኢትዮጵያውያን በሃገራቸው ጉዳይ እንደማይደራደሩ በቅጡ ካለመረዳት የሚመነጭ ነው ብለዋል።
አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስተጓጎል ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚንቀሳቀሱ የውክልና ጦር አስፈፃሚ ቅጥረኛ ኃይሎች መቼም አይሳካላቸውም ማለታቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የፌስቡክ ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
ተጨማሪ ያንብቡ:  የሕወሃት ኃይሎች ስልታዊቷን የደሴ ከተማን መቆጣጠራቸውን ትናንት ቅዳሜ ካስታወቁ በኋላ የመንግስት ኃይሎች በከተማዋ ዛሬ እሁድ አዲስ ውግያ መክፈታቸው ተሰማ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share