ከክረምቱ ጋር ተያይዞ ዛሬ ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ በጣለው በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የጎርፍ አደጋ ተከስቶ በሰዉ ሕይወት እና ንብረት ላይ በደረሰው ጉዳት ማዘናቸውን ከንቲባዋ ገልጸዋል ።
በአስኮ፣ በአደይ አበባ፣ በጀርመን አደባባይና በጎልፍ ክለብ አካባቢዎች በደረሰው ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ እስከአሁን ድረስ መንገዶች ተዘግተዋል፤ የድንገተኛና የእሳት አደጋ ሰራተኞቻችን በቦታዎቹ በመገኘት ሰብዓዊ ጉዳት እንዳይደርስ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኛሉ ብለዋል።
ተጎጂዎችን ወደ ህክምና መስጫ በማጓጓዝና የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ በማድረግ ላይ እንገኛለን ብለዋል።
በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ከክረምቱ ጋር ተያይዞ የጎርፍ አደጋ እንዳይከሰት አስቀድሞ የመከላከል ስራዎችን እየተሰራ ቢሆንም የዛሬው አደጋ ተጨማሪ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ አመላካች መሆኑን ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ጠቁመዋል ።
የብሄራዊ ሜትሮዎሎጂ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በመጪዎቹ ቀናት ከፍተኛ መጠን ያለዉ የዝናብ ስርጭት ስለሚኖር ነዋሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ምክትል ከንቲባዋ ጥሪ ማቅረባቸውን የከተማዋ ፕሬስ ሴክሬታሪያት መረጃ ያመለክታል።
(ኢ ፕ ድ)