ነሀሴ 11 ቀን 2013
ታደሰ መኮንን
ፎቶግራፍ ሀይሉ ሎሌ
የማሰልጠኛ ማዕከሉ ዋና አዛዥ ኮ/ል ዋለልኝ ታደሰ ፣ በትልቅ ሞራልና ወኔ እምቢ ለሀገሬ ብላችሁ ሀገራችሁን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ክቡር የሆነውን የውትድርና ሙያ ለመቀላቀል ከተለያዩ የሀገራችን ጫፍ በመክተታችሁ ኮርቻለሁ ብለዋል ።
ሽብርተኛውን የጁንታ ቡድን ለመደምሰስ በማሰልጠኛ ማዕከላችን የሚሰጡትን ወታደራዊ ስልጠናዎችንና ወታደራዊ ሳይንሶችን ከእውቀት ጋር በመደመር ስልጠናችሁን በተገቢው ሁኔታ በማጠናቀቅ ሀገር ከእናንተ የምትፈልገውን ሁሉ አሟልታችሁ ማገልገል ይጠበቅባችሗል ብለዋል ፡፡