የኢትዮጵያ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀው የኦነግ ሽበርተኛ ቡድን ከትግራይ ሽበርተኛ ቡድን ጋር ወታደራዊ ጥምረት መፍጠሩን አስታወቀ

mero

የኢትዮጵያ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀው ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ጦር በማለት ራሱን የሚጠራው እና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰው የታጠቀ ኃይል ከትግራይ ኃይሎች ጋር ወታደራዊ ጥምረት መፍጠሩን አስታወቀ። በሀገሪቱ አሁን ያለው ብቸኛ መፍትሔ « ይህንን መንግስት ማስወገድ ነው» ለዚህም ከትግራይ ኃይሎች ጋር ጥምረት ፈጥረናል ሲሉ የኦሮሞ ነጻነት ጦር አዛዥ ኩምሳ ዲሪባ ለአሶሽየትድ ፕረስ ነግረዋል።

ጥምረቱ በትግራይ ኃይሎች ሃሳብ አመንጪነት ከጥቂት ሳምንታት በፊት መፈጸሙንም ጨምረው ገልጸዋል። «ጥምረቱ የጋራ ጠላትን በጋራ መፋለም » በሚል መርህ በተለይ ወታደራዊ ትብብር ለማድረግ ከስምምነት መደረሱንም አመልክተዋል። በወታደራዊ ስምምነቱ መሰረት ወታደራዊ መረጃዎችን መቀባበል መጀመራቸውን የገለጹት የታጣቂ ቡድኑ መሪ ለጊዜው ጎን ለጎን ሆነው መዋጋት አለመጀመራቸውን እና ምናልባትም «ያንን የምናደርግበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል» ብለዋል።
ከወታደራዊ ጥምረቱ ጎን ለጎን ከሌሎች የፖለቲካ አጋሮች ጋር ንግግር መጀመራቸውንም ለአሶሽየትድ ፕረስ የነገሩት ኩምሳ ዲሪባ የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድን መንግስት የሚቀናቀኑ እና አጋር መሆን የሚሹ ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገሪቱ እንዳሉም ጠቁመዋል።
በጉዳዩ ላይ የትግራይ ኃይሎች አዛዥ ጄኔራል ጻድቃን ገብረትንሳይ እና ከጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት የተሰጠ ምላሽ እንደሌለ የዜና ምንጩ አክሎ ጠቅሷል። ይሁንና ህወሓት፣ቡድኑን ጨምሮ በኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ላይ ለመወሰን አቅም አላቸው ካላቸው ቡድኖች ጋር ጋር እየተወያየ መሆኑን ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።
«ኢትዮጵያን አሁን ካለበት ቀውስ ለማዳን አቅም ካላቸው ኃይሎች ጋር መተባበር እንዳለብን እናምናለን። ከዛ ጋር የተያያዙ የጀመርናቸው ውይይቶች አሉ። የዛ አካል OLF ሠራዊትም በኢትዮጵያ ውስጥ ስራ እየሰራ ያለ በኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ላይ ለመወሰን አቅም ካላቸው ወገኖች አንዱ ስለሆነ ከኛጋም የጀመርነው ውይይት አለ ከዛ በላይ ብዙ መናገር አልችልም።» ብለዋል። ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ጦር ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድኑ በኢትዮጵያ በህዝብ ብዛት ትልቁን ቁጥር የሚወስደውን ኦሮሚያ ክልል ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ለማጎናጸፍ እንደሚታገል ሲገልጽ ቆይቷል።
ፎቶ ፤ ከማሕበራዊ ትስስር ዘዴዎች የተወሰደ /DW

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: አርበኞች ግንቦት ሰባት በፊኒክስ ያደረገው ሕዝባዊ ስብሰባ እና የሕዝቡ ምላሽ (ልዩ ጥንቅር) * "የኦህዴድ አመራር ሆነው ኦሮምኛ የማይናገሩ አሉ - ኤርሚያስ ለገሰ * * በደቡብ ክልል በኑሮ ውድነቱ ሳቢያ ለአባይ ቦንድ አንከፍልም ሲሉ ተቃውሞ ካሰሙ መምህራን መካከል አስራ አምስቱ ታሰሩ... ሌሎችም

2 Comments

  1. Top Urgent, to Ethiopia Government!!

    It is terrible that but not surprising that TPLF terrorist group request a military assistance and ally with OLF, parts “Onege Sheney” as they have been working quite long time both to vanish historical country Ethiopia. To remind here Ethiopian nice songs or proverb “ይህም ተባሌ እንዴ የምትለውን ጨዋታ ያስታውሰናል፣ ይገርማል!!” These all mess and things happening now due to reluctance made by Ethiopian government as the sabotage has been done by internal administration on supporting both opposition parties.

    So, the government serious action has to continue persistently until these forces vanish once for all from Ethiopian territory. The other miracle press statement is that the spoke person of TPLF message in which since as they are at last stage of defeat, they highly pray for peace full negotiation and support from others.

    Ethiopian government has to make immediate & quick aggressive PR response for what they are propagating and there smart cheating to change the mind of world communities and catch the feeling of their supporters. At this crucial time of uniting Ethiopia those countries, groups or alliance of TPLF shall to think again and again as this is not a war between rebellions and Abyi administration, it is a war of Unity by all Ethiopian people. So every one on the side of such terrorist group has to take care. It is about the war of Unifying Ethiopia!!!

    Long live to Ethiopia!!

  2. አይ ጃልመርሮ ትላንት ኦሮሞ ነገድ ላይ የምድር ሲኦልን ያደረገ በቅርቡ ጌታቸው ረዳ የኦሮሞ ወታደሮችን ለማባረር የተደረገ ቀላል ኦፕሬሽን ነው ብሎ አላግጦብህ ተመልሰህ ጥምረት ፈጥሬያለሁ አልከን አንተስ ላይ የሰራው ቀላል ነው? ምን አይነት ድንዙዛን ናችሁ? በፎቶ ስናያችሁ ትንሽም ቢሆን ሀሳብ ያላችሁ ትመስሉናላችሁ ስትናገሩ ስታስነግሩ ግን ምን ያህል በሀሳብ መጎዳታችሁንና ባዶ መሆናችሁን ያሳያል። በርታ አንዱ ትግሬ አብረህ ተኝተህ እንደ መከላከያ አዘናግቶ እስኪያርድህ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share