በወቅታዊ የአገራችን ጉዳይ… ማን ምን አለ? –

ሰሞኑን ከታሰሩት ጋዜጠኞች እስከ አንዳርጋቸው ጽጌ እና የሙስሊም ኮሚቴዎች ድረስ ሰዎች የየራሳቸውን ሃሳብ እና አስተያየት ይሰጣሉ። እነዚህ ሃሳብ እና አስተያየቶች ሚዛን የሚደፉ ሆነው ስላገኘናቸው፤ ለናንተም ለታሪክም ለህትመት ማብቃቱ መልካም ነው ብለን አሰብን። በመሆኑም የጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ፣ አበበ ገላው አቡ ዳውድ ኡስማን እና ዮናታን ተስፋዬ ያሉትን አቅርበንላችኋል። ከዚህ ቀጥሎ ይነበባል።

ኤልያስ ገብሩ ስለሃብታሙ አያሌው የተናገረው….

ዛሬ በእስር ላይ የሚገኘውን የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የሕዝብ ግንኘነት ኃላፊ የሆነውን ሀብታሙ አያሌውን በሥራ አጋጣሚ ቅርበት አውቀዋለሁ፡፡

በእሱ ላይ የነበረኝን ጥያቄ አቅርቤለትም ደስ ብሎት፣ በዝርዝር መልሶልኝ አስረድቶኛል፡፡ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ‹‹ሀብታሙ ትናንት እንዲህ ነበር፣ እንዲያነው …ወዘተ›› እያሉ ሚዛን የማይደፉ ንግግሮችን ሲናገሩ በእርጋታ አድምጫቸው አውቃለሁ፡፡ ሰዎች ይህንን መሰል ሃሳብ የማንሸራሸር መብት አላቸው ብዬ አምናለሁ፡፡
እኔ ግን፣ ሀብታሙን ሳውቀው ንቁ፣ ብዙ ሃሳቦች ያሉት፣ ስለሀገሩ ያገባኛል የሚል፣ ደፋር ሆኖ ያመነበትን በድፍረት የሚናገር፣ እንደ ንቁ ፖለቲከኛ ለጋዜጠኞች መረጃን በዝርዝር የሚሰጥ፣ ኃይማኖተኛ፣ ፈገግታ የማይለየው፣ ጎበዝ የአደባባይ ፖለቲከኛ የሆነ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡

ለሚነሳለት ሃሳብ ወይም ትችት ሃሳብን በሃሳብ የሚመልስ ልጅነው – ሀብታሙ፡፡
(አንዳንዶች የቀረበላቸውን ሀሳብ ወይም ትችት ፊት ለፊት መመለስ ወይም መሞገት ሲያቅታቸው ወደስድብ እና ዘለፋ ወይም ወዳልታሰበ ሀሳብ ሲነጉዱ እያየሁ ፈገግ እላለሁ፣ እስቃለሁ፣ ከምር ያስቁኛል)
ሃብታሙን ግን ሃሳብን በሃሳብ ከሚመልሱ ውስን የኢትዮጵያ ልጆች መካከል አንዱ ሆኖ አገኘሁትና ደስም አለኝ፡፡ ጠንካራ እና ጀግና ልብስላለውም ወደድኩት!
———————————————–

አበበ ገላው ስለወቅታዊ ሁኔታ የተናገረው…
በአሁኑ ግዜ መታሰር የሚያስፈራበት ግዜ አልፏል። ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ሰው እኛንም እሰሩን እያለ ነው። ሽብረተኛ ተብሎ መከሰስ የሚያስከብር እንጂ የሚያሸማቅቅ መሆኑ ቀርቷል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አብርሃም አለኸኝ ጥሩነህ/ህወሃትን እንደዚህ ተረዳ

የተቃዋሚ ፓርቲዎች በጋራ በሺዎች የሚቆጠሩ አባላቶቻቸውን ሰብስበው እኛም አሸባሪዎች ነን እሰሩን ብለው አደባባይ በየግዜው በተከታታይ እንዲወጡ ቢያደርጉ ብዙ ሰው ፍርሃቱ የበለጠ ይለቀዋል። ለሚታሰሩ ሰዎች እና ለቤተሰቦቻቸው ድጋፍ የሚያደርጉ ስብስቦች በየአካባቢው ሊቋቋሙ ይገባል። አንዱ ሲታሰር ያልታሰረው ድጋፍ ያድርግ። እስኪሚሊዮኖችን ሲያስሩ እናያቸዋለን።

እነርሱ በፍርሃት ሰውን ሁሉ አሸባሪ እያሉ የሚኖርበት ግዜ በጋራ ትግል ማክተም ይገባዋል።

——————————————–

‪አቡ ዳውድ ኡስማን የሙስሊም ኮሚቴዎችን የፍርድ ሂደት አስመልክቶ ያስተላለፈው መልእክት

የኮሚቴዎቻችን እና  የወንድሞቻችን የመከላከያ ምስክር ለፍርድ ቤቱ የማስደመጡ ሂደት በነገው ዕለት ሃምሌ 10 በከፍተኛው ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከዚህ ቀደም ሲካሄድበት ከነበረው ከቃሊቲ 08 አዳራሽ ለውጥ ተደርጎ ከሲ ኤም ሲ አደባባይ ወደ ቀኝ 200 ሜትር ገባ ብሎ ባጃጆች ካሉበት ወደ ቀኝ ታጥፎ ዲቦራ ት/ቤት አካባቢ በሚገኘው በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እንደሚካሄድ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ ይህ ችሎት አዲስ የተገነባ እና ሰፊ የችሎት አዳራሽ እንዳለው ተዘግቧል፡፡

ህዝበ ሙስሊሙም የተለመደውን አጋርነቱን በችሎቱ በመገኘት ለኮሚቴዎቻችን እና ለወንድሞቻችን ሊገለፅ ይገባል፡፡

ፍትህ ለኮሚቴዎቻችን እና ለመላው ሙስሊም ይሁን!!

አላህ ይፈርጃቸው!!

———————————-

ዮናታን ተስፋዬ ስለፍርድ ቤቶች እና የፍርድ ሂደቱ የተናገረው

ፍርድ ቤት ምንም ፍትህ እንደማይገኝ እያወቅነው ለምን ራሳችንን እንደምናታልል አይገባኝም፡፡ ለምን በፍርድ ቤቱና በፍርድ ሂደቱ ተስፋ እንደምናደርግ ልረዳውአልቻልኩም፡፡ ሁሉ ነገር ታፍኖ ሀግ የማያከብር አምባገነን እንኳን ፍርድ ቤት ቀርበው ገና ሳይታሰሩ ውሳኔ አሳልፎ አይናችን ላይ ድራማ እየሰራ እኛ አሁንም ፍርድ ቤት ላይ አይናችን አልተነቀለም፡፡
ለታገቱት ታጋዮች አጋርነትን ማሳየታችን እንደተጠበቀ ሆኖ ፍርድ ቤቱን ትተን ሁላችንም ተራችን ደርሶ እክንታፈን መታገል አለብን፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በ3ቱ የዞን 9 አባላት ፖሊስ ሊመሰረት ያሰበው የሽብርተኝነት ክስ በፍርድ ቤቱ ውድቅ ተደረገ

መታሰር ተራ ነገር እንደሆነ እስካሁን የሄድንበት መንገድ አመላካች ነው፡፡ ስለዚህ በፍርድ ቤት ውሎ ወሬ ጉጉት ከሚገድለን ሀሳባችንና ጉልበታችንን ከምናባክን ለወያኔም ከምንመቸው ትግሉን ማፋፋም ይሻለናል፡፡ ያኔ ሁላችንም ታስረን ሁላችንም ነፃእንወጣለን፡፡ እስከዚያው ጪአማራጭ የለም፡፡ ማንም ለኛ የሚቆምልን የለም እያንዳንዳችን ስለእውነት በፅናት መቆም አለብን፡፡

ራሳችንን ነፃ እናውጣ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share